ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ
35ቱ ዋና ዋና አገልግሎቶች ዝርዝር
1. ፕሮጀክቶችን ማዘጋጀትና መገምገም፤
- የስራ ዕድል መፍጠሪያ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ማዘጋጀትና መገምገም
- ለስራ ዕድል መፍጠሪያ የሚውሉ ፕሮጅቶችን መገምገም
2. የስራ ስምሪት አገልግሎት መስጠት፤
- በተለዩ የስራ ዕድል አማራጮች የስራ ስምሪት አገልግሎት መስጠት፤
3. ስራ ፈላጊዎችን የመመዝገብ አገልግሎት መስጠት፤
- ስራ ፈላጊ ዜጎችን ለመመዝገብ የቅስቀሳና ንቅናቄ ስራዎችን ማከናወን
4. የመረጃ ምክርና ግንዛቤ አገልግሎት መስጠት፤
- የመረጃና የምክር አገልግሎት መስጠት፥
5. ለስራ ፈላጊዎች የቴክኒክና የንግድ ክህሎት ስልጠና አገልግሎት መስጠት፤
- ስራ ፈላጊዎች የሚፈልጉትን የስልጠና አይነት መለየት
6. ስራ ፈላጊዎችን በኢንተርፕራይዝ የማድራጀት አገልግሎት መስጠት፤
- ስራ ፈላጊዎችን በኢንተርፕራይዝ የማድራጀት አገልግሎት፣
- በጥሪት ማፍሪያ የስራ ዘርፍ ላይ የተሰማሩትን ድጋፍ በማድረግ ወደ መደበኛ አደረጃጀት ማሸጋጋር፤
7. አገናኝተው ለሚወጡ ኤጀንሲዎች የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ እና ዕድሳት መስጠት፤
- አገናኝተው የሚወጡ ኤጀንሲዎች የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ መስጠት፣
- አገናኝተው የሚወጡ ኤጀንሲዎች የብቃት ማረጋገጫ ዕድሳት መስጠት፤
8. አገናኝተው የሚወጡ ኤጀንሲዎችን ቁጥጥር ድጋፍና ክትትል ማድረግ፤
- የክትትልና የቁጥጥር ቼክ ሊስቶችን ማዘጋጀት፣
- አገናኝተው ከሚወጡ ኤጀንሲዎች ጋር ተያይዞ የሚነሱ አቤቱታዎችና ቅሬታዎችን መፍታት፥
- ስለውጭ አገር ሥራ ስምሪት እና ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥራዎችን መስራት፤
9. ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት በህዝብ ተሳትፎ ለመደገፍ መድረኮችን በክፍለ ከተማ ደረጃ ማዘጋጀት፤
- የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ስራ የሚሰሩ የተለያዩ አደረጃጀቶችን ማደራጀት፣
- በከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት አፈጻጸም፣ በተገኙ መልካም ልምዶች ዙሪያ በክፍለ ከተማ ደረጃ የምክክር መድረክ ማካሄድ፣
- በክፍለ ከተማ ደረጃ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎችን የልየታ ስራ ለመስራት ወረዳዎችን መደገፍ፤
- የተጠቃሚዎች ማህበራዊ አገልግሎት ትስስር ስራ መስራት
- በልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚነት የማህበራዊ ተጠያቂነት ማስፈን
10. የቅሬታና አቤቱታ ስርአት መዘርጋት፤
- በክፍለ ከተማ ደረጃ የቅሬታ ምንጮችን መለየት የመፍትሄ ሀሳብ ማመንጨትና ስልጠናዎችን መስጠት፤
11. የማህበረሰብ አቀፍ ስራ ተጠቃሚዎች ሊያሰራ የሚያስችል ቦታ በመስለየት ማሰራትና ተጠቃሚ ማድረግ፤
- በክፍለ ከተማ ደረጃ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች መረጃ በዩፓስ ማደራጀት፤
- በአካባቢ ልማት ስራዎች ጋይድላይን ላይ ስልጠና መስጠት
- በክፍለ ከተማ ደረጃ የማህበረሰብ ልማት ስራዎች ሰሪ ሀይሎችን ወደ ስራ ማስገባት፣ በማሰራት፣ ተጠቃሚ ማድረግ እና ድጋፍና ክትትል ማድረግ
12. የኑሮ ማሻሻያ የድጋፍ ማዕቀፎች መስጠት፤
- የኑሮ ማሻሻያ ተጠቃሚዎች ተጨማሪ ጥሪት ማፍሪያ ላይ ማሰማራት፣
- የኑሮ ማሻሻያ ተጠቃሚዎች በተለያዩ የግብርና እና ከግብርና ውጪ ባሉ የገቢ ማስገኛ ስራዎች እንዲሰማሩ እና ጥሪት እንዲጨምሩ ማድረግ
- የአካባቢ ልማት ስራዎች ከቤተሰብ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻያ ስራዎች እና ከሰርዓተ-ምግብ ጋር በማስተሳሰር ተግባራዊ ለማድረግ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት
- የኑሮ ማሻሻያ ተጠቃሚዎች አዋጭ የስራ ዘርፍ ላይ የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ
- የኑሮ ማሻሻያ የድጋፍ ማእቀፎችን እንዲያገኙ ማድረግ፤
13. የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን ማቋቋም ና ማጠናከር፤
- የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ማጠናከር
- የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት እና በአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ መሰረት እንዲፈፀም ማድረግ
- ለአንድ ማዕከላት በፍረጃው መሰረት የማበረታቻ፣ እውቅና እና ሽልማት አሰራርን መዘርጋት፤
- የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ የህግ ማዕቀፎች (ደንብ፤ መመሪያ፣ የማስፈጽሚያ ማንዋሎችን) መገምገምና ግብዓት መስጠት
- የአንድ ማዕከላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፤
- የአገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍና ለማዘመን በቴክኖሎጅ የተደገፈ የአሰራር ስርዓቶችን መዘርጋት የሚያስችል ግብዓ መስጠጥ
- የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ግንባታዎችን ክትትል ማድረግ፤
- በተለያዩ ሴክተር መስሪያቤቶች ለስራ ፈላጊዎችና ለኢንተርፕራይዞች የሚሰጡ አገልገሎቶችን በአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ውስጥ እንዲሰጡ ማድረግ፤
14. ስልጠና የሚሰጡባቸውን ስርዓተ ስልጠና የማሰልጠኛ ማቴሪያሎች (ሞጁሎች) ማሰራጨት፤
- ስልጠና የሚሰጡባቸውን ስርዓተ ስልጠና የማሰልጠኛ ማቴሪያሎች (ሞጁሎች) ማሰራጨት
15. ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
- በክፍለ ከተማ ደረጃ በልማታዊ ሴፍቲኔት የፕሮጀክት ማበልጸጊያ እና ማስተግበሪያ ሰነድ ዙሪያ ለአመራርና ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት
- ለሚሰሩ የአካባቢ ልማት ስራዎች የሴፍጋርድ/ማህበራዊና አካባቢያዊ ደህንነት/ መጠበቅ ስራ መስራት
- በፕሮጀክቱ የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠቃሚዎችን ወደ ስራ ማስገባት
- በክፍለ ከተማ ደረጃ የመሰረተ ልማት ግንባታ ግብዓት ፍላጎት መለየት
- የኑሮ ማሻሻያ ተጠቃሚ ቤተሰቦችን እና የገንዘብ ስጦታ የሚያገኙ ተጠቃሚዎችን መለየት
16. የፕሮግራም ማደስ ፤ማስፋፋት እና ዕውቅና የማግኘት አቅማቸውን ማሳደግ፤
- ከየቤተሰቡ አንድ ተወካይ እንዲመርጡ ለማድረግ ግንዛቤ በመፍጠር እንዲለዩ ማድረግ
- በኑሮ ማሻሻያ የድጋፍ ማዕቀፎች ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፤
17. በተቋማትና ሰልጣኞች ያሉ አለመግባባቶች በጋራ እንዲፈቱ ማድረግ፤
- በግል ለመስራት የሚፈልጉትን ተጠቃሚዎች የመለየት ስራ በመስራት የስራ ፍለጋ እቅድ እንዲያቅዱ ማድረግ
- ቴክኒካል ስልጠና የሚያስፈልጋቸውን የኑሮ ማሻሻያ ተጠቃሚዎችን ስልጠናውን እንዲያገኙ ማድረግ
18. የሱፐርቪዥን እና ቁጥጥር አገልግሎት መስጠት፤
- ለተጠቃሚዎች በሰለጠኑት የስራ ዘርፍ የብቃት ማረጋገጫ /COC/ እንዲያገኙ አሰራር ስርዓት መዘርጋት
19. ከኢንዱስትሪውና ባለድርሻ ጋር ትስስር በመፍጠር የውጤት ተኮር ስርዓቱን ማጎልበት፤
- የምክርና እና ድጋፍ አገልግሎት ሞጁል ዙርያ መስጠት፥
- የኑሮ ማሻሻያ የገንዘብ ስጦታ/Grant/ የሚያገኙ ተጠቃሚዎችን ለመለየት ዝግጅት ማድረግ
- የኑሮ ማሻሻያ ተጠቃሚዎች የፋይዳ ግምገማ ማድረግ፤
20. ቀልጣፋ የመረጃ ልውውጥ ስርአት መዘርጋትና ማስተዳደር፤
21. የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የህግ ማእቀፎች ተፈጻሚነት ለማረጋገጥና የሙያ ደህንነትና ጤንነት መጠበቁን ለመከታተል ቁጥጥር ማድረግ፤
- የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ የህግ ማዕቀፎች ተፈፃሚነት ማረጋገጥ፤
- የሠራተኞች ደህንነት፣ጤንነትና የስራ አካባቢ እንዲጠበቅ ማድረግ
22. በህግ ማእቀፎች ፖሊሲዎች እና በሙያ ደህንነት ጤንነት አጠባበቅ የአቅም ግንባታ ስልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ መስራት፤
- የፖሊሲና የህግ ማዕቀፎች ላይ ግንዛቤ ማስጨበጥ
- በሙያ ደህንነትና ጤንነት አጠባበቅ ግንዛቤ ማስጨበጥ
- የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚመለከቱ የዓለም አቀፍ ክብረ በዓላትን በኢንዱስትሪው ማህበረሰብ ንቅናቄ በመፍጠር ማክበር
23. የሥራ ሁኔታ መረጃ መሰብሰብ፣ማደራጀት፣መተንተንና ስታትስቲካል መጽሄት በማዘጋጀት ማሰራጨት፤
- ለሴፍቲ ኮሚቴ ምዝገባና እውቅና መስጠት
- የአሠሪና ሠራተኛ ማህበራት ምዝገባና እውቅና አገልግሎት መስጠት፤
- የህብረት ስምምነት ምዝገባና ዕውቅና አገልግሎት መስጠት
24. በስራ ቦታ የማህበራዊ ምክክር አሠራሮች ማስተግበር፤
- የሚቀርቡ የወል የሥራ ክርክሮችንና የህብረት ድርድር ልዩነቶች በስምምነት እልባት እንዲያገኙ ማድረግ
- ድጋፍና ክትትል ማድረግ
- በሥራ ሁኔታዎች ላይ ያተኮሩ ጥናቶች ማካሄድ
- በማህበራዊ ምክክር አሠራር ጥናት ማካሄድ
25. የማምረት አቅም አጠቃቀም መለካት፤
26. የድርድርና የኮሚሽንኒንግ አገልግሎት መስጠት፤
- የማሽን ተከላ ሂደትን ማማከር
27. የካፒታል ሊዝ ድጋፍ እንዲያገኙ ማመቻቸት፤
28. የመስሪያ፣ ማሳያ እና መሸጫ ቦታ ማመቻቸት፤
- ለኢንተርፕራይዞች የመስሪያ፣ ማሳያ እና መሸጫ ቦታ ማመቻቸት፤
- የመስሪያ ቦታ ተስማሚነት ልየታ ማድረግ ላይ ድጋፍ መስጠት
- የዘርፍ ማህበራትን ማደራጀት፤
29. የፋይናንስ ድጋፍ እንዲያገኙ ማመቻቸት፤
- የንግድ ስራ እቅድ/ቢዝንስ ፕላን መገምገም
30. የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ገበያ ትስስር መፍጠር፤
- የሀገር ውስጥ ገበያ ትስስር መፍጠር
- ኢንተርኘራይዞች የውጭ ሀገር ገበያ ትስስር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማመቻቸት፤
31. ምርትና አገልግሎትን ማስተዋወቅ፤
- ኤግዚቢሽንና ባዛር ማዘጋጀት
- የኢንተርፕራይዞችን ምርትና አገልግሎት በኢምፖሪየም /በምርት ማሳያና መሸጫ ሱቆች/ በማስገባት አንዳስተዋውቁና እንዲሸጡ ማድረግ
- በሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበራት ሱቅ ምርትና አገልግሎት እንዲያስተዋውቁና እንዲሸጡ ማድረግ
- ዳይሬክተሪ እና ካታሎግ በማዘጋጀት የኢንርፕራይዞችን ምርትና አገልግሎት ማስተዋወቅ
32. የግብዓት ትስስር መፍጠር፤
- የግብዓት እና የምርት ትስስር ማመቻቸት
33. የዕድገት ደረጃ ሽግግር አገልግሎት መስጠት፤
- የዕድገት ደረጃ ሽግግር መስጠትና መረጃቸውን ማደራጀት
- የተሰጠዉ የዕድገት ደረጃ ሽግግር ትክክለኛነት በዳሰሳ ጥናት ማረጋገጥ
- ወደ ከፍተኛ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞችን ማስመረቅ
34. የኦዲት አገልግሎት መስጠት፤
- የኦዲት አገልግሎት ለመስጠት መረጃ መሰብሰብ
35. ምርጥ ተሞክሮዎችን መቀመርና ማስፋት፤
- የሀገር ውስጥ ምርጥ ተሞክሮ መቀመር
- ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን መለየት
- ምርጥ ተሞክሮ መለየት
- የውጪ ሀገር ምርጥ ተሞክሮ መቀመር
- ምርጥ ተሞክሮ ማስፋት
- የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣
- ክትትል እና ድጋፍ ማድረግ